ሃይማኖት መሢሐዊት ክፍል ሁለት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!

                          ሃይማኖት መሢሐዊት ክፍል ሁለት

በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ዉሉደ እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ መንፈሳዉያን የተሰኛችሁ ማኅበረ መሢሐውያን እንደምን ሰነበታችሁ እንደምን አላችሁ እንደምንስ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ደረሳችሁ?አሜን እግዚአብሔር ይመሥገን ብለን ስሙን በኃጢአተኛ አንደበታችን እድንጠራው የወደደና የፈቀደ ልዑለ ባሕርይ ቅዱስ እግዚአብሔር በፈጠረው ፍጥረት አንደበት ሁሉ ስሙ ከአጽናፈ ዓለም እስከ ዓጽናፈ ዓለም ፣ ከአድማስ እስከ አድማስ ፣ ከበርባሮስ እስከ ጽርሐ  አርዓያም ድረስ የተመሰገነ ይሁን ፡፡ እሱን ጠርተን እሷን የማንተዋት የንጽኅናችን መሠረት የጽድቃችን አክሊል ፤ በካሮቹ ዘንድ ያለ ስማችን ስም የተሰጠንባት (ተቀባት ይላሉ እያሉ የሚናሩባት) አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች መልዕልተ ፍጡራን መትሕተ ፈጣሪ የሆነች ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሐን ክብርት ድንግል ማርያም አምላክ በሰጣት ክብር መጠን የተመሠገነች ትሁንልን ፡፡ ጻድቃን ሰማዕታት ፣ ደናግል  መነኮሳት ፣ ነቢያት ሐዋርያት ፣ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔር አምላክ በሰጣቸው ጸጋ መጠን የተመሰገኑ ይሁኑ ፡፡
የዛሬው መልእክት ሳይማሩ አስተማሪ ነን እያሉ የሚናገሩየግቢ ጉባዔመደዴዎች ለአእምሯቸው እና ለልቡናቸው ያልተረዱትን እኛ እደተሳሳትን አድርገው የሚናገሯቸውን ጉዳዮች በማንሳት ኦርቶዶክሳዊት መልስን መስጠት ይሆናል ፡፡ በጥሙና ተከታተሉኝ ፡፡

ሃይማኖት መሢሐዊት ‹ ክፍል አንድ›


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ!

ሃይማኖት መሢሐዊት  ‹ ክፍል አንድ›
በክርስቶስ ክርስቲያን በወልድ ዉሉደ እግዚአብሔር በመንፈስ ቅዱስ መንፈሳዉያን የተሰኛችሁ ማኅበረ መሢሐውያን እንደምን ሰነበታችሁ እንደምን አላችሁ እንደምንስ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ደረሳችሁ?አሜን እግዚአብሔር ይመሥገን ብለን ስሙን በኃጢአተኛ አንደበታችን እድንጠራው የወደደና የፈቀደ ልዑለ ባሕርይ ቅዱስ እግዚአብሔር በፈጠረው ፍጥረት አንደበት ሁሉ ስሙ ከአጽናፈ ዓለም እስከ ዓጽናፈ ዓለም ፣ ከአድማስ እስከ አድማስ ፣ ከበርባሮስ እስከ ጽርሐ  አርዓያም ድረስ የተመሰገነ ይሁን ፡፡ እሱን ጠርተን እሷን የማንተዋት የንጽኅናችን መሠረት የጽድቃችን አክሊል ፤ በካሮቹ ዘንድ ያለ ስማችን ስም የተሰጠንባት (ተቀባት ይላሉ እያሉ የሚናሩባት) አምላክን በድንግልና ጸንሳ በድንግልና የወለደች መልዕልተ ፍጡራን መትሕተ ፈጣሪ የሆነች ቅድስተ ቅዱሳን ንጽሕተ ንጹሐን ክብርት ድንግል ማርያም አምላክ በሰጣት ክብር መጠን የተመሠገነች ትሁንልን ፡፡ ጻድቃን ሰማዕታት ፣ ደናግል  መነኮሳት ፣ ነቢያት ሐዋርያት ፣ ቅዱሳን መላእክት እግዚአብሔር አምላክ በሰጣቸው ጸጋ መጠን የተመሰገኑ ይሁኑ ፡፡

“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል ዐራት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ !
“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል ዐራት
==============+==============
“ሰላም ለክሙ ወጸጋ ለእግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ ነአኵቶ ለእዚአብሔር አቡሁ ለእዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘልፈ በእንቲአክሙ፤ ወንጼሊ እምአመ ታፈቅርዎሙ ሰማዕነ ሃይማኖተክሙ በኢየሱስ ክርስቶስ ወዘከመ ታፈቅርዎሙ ለኵሎሙ ቅዱሳን ፤ በእንተ ተስፋክሙ ዘሥዩም ለክሙ በሰማያት ዘአቅደምክሙ ሰሚዐ በቃለጽድቅ ትምርተ ወንጌል
ሰላም ለእናንተ ይሁን የአባችን የእግዚአብሔር የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይደርባችሁ ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ እግዚአብሔርን ዘወትር ስለ እናንተ እናመሰግነዋለን ፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመናችሁንና ቅዱሳንን ሁሉ መውደዳችሁን ከሰማንበት ጀምሮ እንጸልያለን ፡፡ የእውነት ቃል በሆነው በወንጌል ትምርት አስቀድሞ ስለ ሰማችሁት በሰማያት ስለ ተዘጋጀላችሁ ስለተስፋችሁ” ቆላ ምዕ 1 ቁ 2-5 ፡፡
ወንድም እህቶቼ መሢሐውያን እደምን ሰነበታችሁ? ከመጻሕፍት ዓለም የራቁ  ዘላን የምድረበዳ እንግዶች አማናዊ መሢሕ ኢየሱስ ክርስቶስ መሢሕ ወበኩረ ምእመናን የተሰኘባትን እውነት ሙጥጥ ጭልጥ አድገው ክደው የራሳቸው መካድ ሳያንስ ማንም ሳይነካቸው ማንም ሳያስገድዳቸው ቤታችንን ለነኩን ዉልደ መጥባሕት በሙሉ ኦርቶዶክሳዊ መልሳችንን እንሰጣቸው ዘንድ ተገቢ በመሆኑ በባለፈው በክፍል አንድ ላይ ስሙን የጠቀስኩለት እንግዳችን/ ሁነኛው ተሾመየጻፈውን ጦማረ ክሕደት መሠረት አድርጌ ክፍል ዐራትን እደሚከተለው ጻፍኩላችሁ፡፡

1ኛ‹‹‹‹‹“ሥላሴ በከዊን ከመገናዘብ በቀር አንዱ አካል በአንዱ አካል አያድርም ፡፡ አንዱም ለሌላው ክብር አይሆንም በክብር ዕሩያን ናቸውና” ብሏል በክሕደት ጽሁፉ

“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል ሦስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ !

“የተቀብዐ እንግዶች” 
==============+==============
“ሰላም ለክሙ ወጸጋ ለእግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ ነአኵቶ ለእዚአብሔር አቡሁ ለእዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘልፈ በእንቲአክሙ፤ ወንጼሊ እምአመ ታፈቅርዎሙ ሰማዕነ ሃይማኖተክሙ በኢየሱስ ክርስቶስ ወዘከመ ታፈቅርዎሙ ለኵሎሙ ቅዱሳን ፤ በእንተ ተስፋክሙ ዘሥዩም ለክሙ በሰማያት ዘአቅደምክሙ ሰሚዐ በቃለጽድቅ ትምርተ ወንጌል
ሰላም ለእናንተ ይሁን የአባችን የእግዚአብሔር የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይደርባችሁ ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ እግዚአብሔርን ዘወትር ስለ እናንተ እናመሰግነዋለን ፡፡

“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል ሁለት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ !

“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል ሁለት
==============+==============
“ሰላም ለክሙ ወጸጋ ለእግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ ነአኵቶ ለእዚአብሔር አቡሁ ለእዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘልፈ በእንቲአክሙ፤ ወንጼሊ እምአመ ታፈቅርዎሙ ሰማዕነ ሃይማኖተክሙ በኢየሱስ ክርስቶስ ወዘከመ ታፈቅርዎሙ ለኵሎሙ ቅዱሳን ፤ በእንተ ተስፋክሙ ዘሥዩም ለክሙ በሰማያት ዘአቅደምክሙ ሰሚዐ በቃለጽድቅ ትምርተ ወንጌል
ሰላም ለእናንተ ይሁን የአባችን የእግዚአብሔር የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይደርባችሁ ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ እግዚአብሔርን ዘወትር ስለ እናንተ እናመሰግነዋለን ፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመናችሁንና ቅዱሳንን ሁሉ መውደዳችሁን ከሰማንበት ጀምሮ እንጸልያለን ፡፡ የእውነት ቃል በሆነው በወንጌል ትምርት አስቀድሞ ስለ ሰማችሁት በሰማያት ስለ ተዘጋጀላችሁ ስለተስፋችሁ” ቆላ ምዕ 1 ቁ 2-5 ፡፡

ወንድም እህቶቼ መሢሐውያን እደምን ሰነበታችሁ?ከመጻሕፍት ዓለም የራቁ  ዘላን የምድረበዳ እንግዶች አማናዊ መሢሕ ኢየሱስ ክርስቶስ መሢሕ ወበኩረ ምእመናን የተሰኘባትን እውነት ሙጥጥ ጭልጥ አድገው ክደው የራሳቸው መካድ ሳያንስ ማንም ሳይነካቸው ማንም ሳያስገድዳቸው ቤታችንን ለነኩን ዉልደ መጥባሕት በሙሉ ኦርቶዶክሳዊ መልሳችንን እንሰጣቸው ዘንድ ተገቢ በመሆኑ በባለፈው በክፍል አንድ ላይ ስሙን የጠቀስኩለት እንግዳችን/ ሁነኛው ተሾመየጻፈውን ጦማረ ክሕደት መሠረት አድርጌ ክፍል ሁለትን እደሚከተለው ጻፍኩላችሁ፡፡
1ኛ‹‹‹‹‹ “ወእንዘ ኢይትዌሰክ ክብረ እንዘ እግዚአብሔር ውእቱ ነሥአ ሥጋ” ድ/ቄ ምዕ 26 ዘዮሐንስ ኤጲስ ቆጶሰ ክፍል 7” በማለት ጠቅሷል።

“የተቀብዐ እንግዶች” ክፍል አንድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ !
==============+==============
“ሰላም ለክሙ ወጸጋ ለእግዚአብሔር አቡነ ወእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ፤ ነአኵቶ ለእዚአብሔር አቡሁ ለእዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘልፈ በእንቲአክሙ፤ ወንጼሊ እምአመ ታፈቅርዎሙ ሰማዕነ ሃይማኖተክሙ በኢየሱስ ክርስቶስ ወዘከመ ታፈቅርዎሙ ለኵሎሙ ቅዱሳን ፤ በእንተ ተስፋክሙ ዘሥዩም ለክሙ በሰማያት ዘአቅደምክሙ ሰሚዐ በቃለጽድቅ ትምርተ ወንጌል
ሰላም ለእናንተ ይሁን የአባችን የእግዚአብሔር የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይደርባችሁ ፡፡ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባቱ እግዚአብሔርን ዘወትር ስለ እናንተ እናመሰግነዋለን ፡፡ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመናችሁንና ቅዱሳንን ሁሉ መውደዳችሁን ከሰማንበት ጀምሮ እንጸልያለን ፡፡ የእውነት ቃል በሆነው በወንጌል ትምርት አስቀድሞ ስለ ሰማችሁት በሰማያት ስለ ተዘጋጀላችሁ ስለተስፋችሁ” ቆላ ምዕ 1 ቁ 2-5 ፡፡

ባሕረ ሐሳብ ክፍል ሁለት

ቀመር ማለት ማስላት ፣ መቁጠር ማውጣት ማለት ነው ፡፡ ቀመርም ጥንታትን መሠረት ያደረገ ነው ፡፡ ጥንት ማለትም ለዘመን መቆጠር መሠረት የሆነ ማለት ነው ወይም መነሻ መጀመሪያ ማለት ነው ፡፡ እነዚህም ሦስት ናቸው ፡፡ ምን ምን ቢሉ ፤ አንድ ዓለም የተፈጠረችበትን ቀን ዕለት እሑድ ሲሆን ፤ ይኸውም ጥንተ ዕለት ይባላል ፡፡ አንድም አትክልት ዕፅዋት ተፈጥረው ዕድሜ የተቆጠረላቸውን ቀን ዕለት ሠሉስ ሲሆን ፤ ይኸውም ጥንተ ቀመር ይባላል ፡፡ 

አንድም ፀሐይ ፣ ጨረቃ ከዋክብት የተፈጠሩበት ዕድሜም መቆጠር የተጀመረባቸውን ቀን ዕለት ረቡዕ ሲሆን ፤ ይኸውም ጥንት ዖን ይባላል ፡፡ ዖን ማለት ብርሃን ማለት ነው ፡፡ በዚህ መሠረት መታሰቢያ ቀመርን ለመስፈረያ ወይም ለመቁጠሪያ የሚያገለግሉት ሰባት(፯) ናቸው ፡፡ ከምን አገኘነው ቢሉ ፤ አቡሻሕር “ወሤሞ በመካነ ቀዳማይ ዕለታት ዓመት ወርኃዊት ፤ ወበመካነ ዕለተ ኍልቊ ኬክሮስ ፤ ወበመካነ ኬክሮስ ኍልቊ ካልዒት ፤ ወበመካነ ካልዒት ኍልቊ ሣልሲት ፤ ወበመካነ ሣልሲት ኍልቊ ራብዒት ፤ ወበመካነ ራብዒት ኍልቊ ኃምሲት ፤ ወበመካነ ኃምሲት ኍልቊ ሳድሲት ብሎዋልና ፤ ይኸን መሠረት አድርገን ቀመርን የምንሰፍርባቸው 7 ናቸው ፡፡ 

ባሕረ ሐሳብ ክፍል አንድ


ባሕረ ሐሳብ ማለት ቁጥር ያለው ዘመን ማለት ነው ፡፡ እንዴት ቢሉ ፤ ባሕር ዘመን ፣ የተቆጠረ ተብሎ ይተረጎማልና ፤ ይህስ ከምን እናገኘዋለን ቢሉ ፤ ዕዝራ ሱቱኤል ተናግሮታል ፡፡ ይኸውም “ይህ ዓለም በሚዛን ተመዝኗልና ፤ ባሕሩንም በመስፈሪያ ሰፍሮታልና ፤ የተሰጠውንም መስፈርት እስኪፈፀም ድረስ ዝም ይላል ፤ አይነቃምም (ምዕ 2 ቊ "7)” በማለት ባሕር የተቆጠረ ፤ ዓለምም የተመዘነች ፤ የተለካች መሆንዋን እግዚአብሔር በነቢያት አድሮ ገልፆልናል ፡፡
ባሕርን በመስፈሪያ ቆጥሮታል ካልን መስፈሪያውንስ ለማን ገለጸው ቢሉ ፤ መቁጠሪያ ዘመንንስ በሱባኤ ፣ በኢዮቤልዩ እንዲቆጥር ለአዳም (ሱባኤ አዳም) ፤ መስፈሪያንም ለሄኖክ ሰጥቶታል ፡፡ 

ሐሳብስ ማን ቁጥር አለው ቢሉ ፤ ቅዱስ ዳዊት ነው ፡፡ ምን አለው ቢሉ ፤ “ብፁዓን እለ ተኀድገ ሎሙ ኃጢአቶሙ ፤ ወእለ ኢሐሰበ ሎሙ ኵሎ ጌጋዮሙ ፤ ብፁዕ ብእሲ ዘኢኈለቈ ሎቱ እግዚአብሔር ኃጥአቱ (ኀጥአታቸው ይቅር የተባለላቸው ብፁዓን ናቸው ፤ በደላቸውንም ኹሉ ያልቆጠረባቸው ፤ እግዚአብሔርም ኃጢአቱን ያልቆጠረበት ሰው ብፁዕ ነው” እንዳለ (መዝ " ቊ -2) ፡፡ ስለዚህም ባሕር ሐሳብ ማለት ቀድሞ የነበረ ፣ አሁንም ያለ ፣ ለወደፊትም የሚኖር ዘለዓለማዊ እግዚአብሔር በዚች ባለንባት ዓለም ሌሊቱንና ቀኑን እያፈራረቀ የሚመግብ እግዚአብሔር መሆኑን በቁጥር ፣ በስፍር መዝኖ የሚያስረዳ ማለት ነው ፡፡
ባሕር ሐሳብ በስንት መንገድ እናየዋለን እንተ

ውሉደ ይሁዳ (ክፍል ሁለት)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ  አምላክ አሜን!
==========================================
በባለፈው በክፍል አንድ መልእቴ “ዐራት ዓይናው” አባ “ሰሎሞን ዳዊት” “ቅባትን በእሳት” የምትል የጨዋ ንግግርን በተናሩባት ወቅት እሳትን በእሳት የሚል ሀሳብን ማንሳታቸውንና ዐራት ዓይናው አንድ ዓይና እንኳን የማያስብላቸውን ነገር መናገራቸውንና እንደይሁዳ አምላካቸው መንፈስ ቅዱስን እየሰደቡ በ30 ብር እየቸበቸቡ የሚገኙ መሆናቸውን በሐተታ አንስቼ መዘከሬ ይታወሳል ፡፡ እነሆ በቀጠሮየ መሠረት ዛሬ ደግሞ በመጽሐፏ ውስጥ ብዙውን ስፍራ የያዘው “ተዋሕዶ ሃይማኖታችን” የሚል ቃል አንስቼ እንድንወያይ አምላክ በፈቀደልን መጠን ይህችን ጽሁፍ እንካችሁ ብያለሁ፡፡  

ውሉደ ይሁዳ (ክፍል አንድ)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ይድረስ  ለ “ሊቀ ሊቃውንት”  ሰሎሞን ዳዊት
=================
በ21ኛው መቶ ክፍለዘመን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በምሥራቃዊት ጎጃም ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር (መቀመጫውን ደብረ ማርቆስ ባደረገው) የዐራቱ ጉባዔ መምህር ተብለው የሚጠሩት መሪጌታ ሰሎሞን ዳዊት "ቅባትን በእሳት" የምትል ርእስ ያላት በዋጋዋ ክርስቶስን እንደሸጠ እንደይሁዳ መንፈስ ቅዱስን በ30 ብር የምትሸጥ መጽሐፍ ጽፈዋል ፡፡ እጅጉን የሚደንቀው ደግሞ ግሱንም ይሆን ከግሱ የሚወጣውን ሳቢ ዘር የማይለዩ ጨዋ ሰው ሁነው ሳገኛቸው ፤ ስማቸውና ማንነታቸው የማይገናኙ መሆናቸው የበለጠ ግልጽ ይሆናል ፡፡ “እሱም ቅባትን በእሳት” የሚል ነው ፡፡

“ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ” ክፍል ሦስት

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽክፍል ሦስት
ይድረስ “Habtamu St”››››››ለሚሉህ ግለሰብ በአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ ለጻፍክልኝ ጥያቄ መልስ
======================================
1‹‹‹‹‹‹ፊቴ እንዲያበራ እናቴ የቀባችኝ ቅባት፣
ካደረገኝ አምላክ ዘበምድር ወዘበሰማያት፣
የቅቤ መገኛ ላማችን እርሷም ድንቅ አምላክ ናት”›››››››››
ብለህ ለተናርካት ንግግርህ መልሴን በስንኝ ቋጠሮ
አስልተው ካልሰጡት ማረሚያና አራሚ
ንፍጥ ይለቀልቃል አላዋቂ ሳሚ፡፡
እንዳሉን አባቶች በሥነ ቃላቸው፤
ሰምተኸው ለማታውቅ ለአንተ ለእንግዳው፡
ጣዕመ ምሥጢሩ የቅብዓት ምሳሌው
መስሎ ይታይሃል ቅቤ ምናምኑ የላም የፍየሉ የግመል የአህያው፡፡
ዳሩ ግን ወዲህ ነው ድንቅ ንግግሩ፡
የተቀብዐ ዳገት ናሙና ምሥጢሩ፡፡
የሥላሴ ሕይወት መንፈሰ ቅግዚአብሔር፡
በላሞቹ ዉጤት በቅቤ በከንቱው
የሚለካ አይደለም አምላክ ዘለዓለም ነው፡፡
በትምርት ታጥቦ ዓይንን ካልገለጡ፤
ወደ መምህርነት ምንም ቢያንጋጥጡ
የተቀብዐ ዳገት የተሰብአ መውጫ፤
ከቶ አይገኝም በትዕቢት በአፍ ብልጫ፡፡
ብየሀለሁ፡፡

 “ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ” ክፍል ሁለት፡፡

                                                               በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ

 “ሲያምኑ ግማሽ ሲተረጉሙ ዳሽ” ክፍል ሁለት

ይድረስ Habtamu St”››››››ለሚሉህ ግለሰብ 

በአስተያየት መስጫ ሳጥን ላይ ለጻፍክልኝ ጥያቄ መልስ

መናገር ስለምንችል ብቻ ባንናገር መልካም ነው፤እኛ ተበላሽተን ሰውም እያበላሸን ነው”›››››››ብለሃል አዎ ወንድሜ ተበላሽታችሁ ትውልዱን አታበላሹት ነው የእኔም መልእክቴ

1‹‹‹‹ “በቅባት ነገሰ ማለት እየሱስን የባህሪ አምላክ ያሰኘዋል?”›››››› ”ዘአንገሦ ለሥጋ አዳም በመንፈስ ቅዱስ ወረሰዮ ቅዱሰ ወማኅየዌ--የአዳምን ባሕርይ በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት ያከበረው የባሕርይ አምላክም ያደረገው እሱ ነው” .አበው ዘእልሥጦ አግአያ 25

2‹‹‹‹‹‹‹‹ “.የባህሪ አምላክነትን እያነሳህ ሁለተኛ ከአብ ተቀበለ ማለት ፍጡርነትን አያሳይም?ሶስት ልደት አለዴ?አብ ሁለቴ ወለደው?ስላሴ ዘጠኝ ይሆናል እዴ?”›››››››››››ወንድሜ የባሕርይ አምክ መሆኑን የምታን ከሆነ  የባሕርይ አምላክ ሰው ሁኖ የሰውነትን ገንዘብ(መቀበልንበተዋሕዶ ገንዘቡ በማድረጉ  በሰውነቱ ተቀበለ “ወበከመ ለአብ ቦቱ ሕይወት ኀቤሁ ከማ ለወልድኒ ወሀቦ ሕይከወት ከመ ይኩን ሕይወት ኀቤሁ--ለአብ በራሱ ሕይወት እዳው እንዲሁ ለወልድም ሕይወት ይኖረው ዘንድ ሕይወት ዘጠው….እስመ ወልደ እግዚአብሔር ኮነ ወልደ እጓለእመሕያው” ዮሐ 5 26-27 ብሎ ተናገረለት፡፡

ሲያምኑ ፡ ግማሽ ፡ ሲተረጉሙ ፡ ዳሽ


በስመ ፡ አብ ፡ ወወልድ ፡ ወመንፈስ ፡ ቅዱስ ፡ አሐዱ ፡ አምላክ ሲያምኑ ፡ ግማሽ ፡ ሲተረጉሙ ፡ ዳሽ ፡ ይህች ፡ ብሂል ፡ “የነሲብ ፡ ትርጓሜ” ፡ ብለን ፡ እንመለከታለን ፡፡

===============================================
በኢትዮጵያ ፡ ኦርዶክሳዊት ፡ ቤተክርስቲያን ፡ ውስጥ ፡ የሚገኙ ፡ “በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ወልድ ፡ ቅብዕ” ፡ ብለው ፡ የሚያምኑ ፡ ልዮናውያን ፤ የወልደ ፡ እግዚአብሔርን ፡ አምላክነት ፡ እናምናለን ፤ ተዋሕዶንም ፡ እንከተላን ፣ ይባስ ፡ ብሎም ፡ ስማችን ፡ ተዋሕዶ ፡ ነው ፡ ሲሉ ፡ ይደመጣሉ ፡፡ እነኝህ ፡ ሰዎች ፡ ተዋሕዶን ፡ እናምናለን ፡ እያሉ ፡ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ ወልድ ፡ ቅብዕ ፡ ማለትን ፡ ዘንቀው ፡ ቀላቅለው ፡ ያስተምራሉ ፡ ይደናበራሉም፡፡ ያም ፡ ሆነ ፡ ይህ ፡ ተዋሕዶና ፡ በተዋሕዶ ፡ ከበረ ፡ በመጻሕት ፡ ምሥጢርም ፡ ይሁን ፡ በቋንቋ ፡ ሕግ ፡ አንድ ፡ አይደሉም ፡ ልዩነታቸውም ፡ የሰማይና ፡ የምድር ፡ ያህል ፡ ነው፡፡