የተቀብዐ ጾመኞችና ሩጫቸው

                        ክፍል ሦስት 

“ዘተወልደ በዳኃሪ መዋዕል በሥጋ ፤ ወተቀብዓ ውስተ ዝንቱ ዓለም በዘይትፌኖ እምኀበ እግዚአብሔር አብ ወተሰምየ ክርስቶስ ፡፡ አኮ በእንተ ካልዕ አላ በእንተ ዘተቀብዓ ፤ እስመ ክርስቶስ ብሂል ቅቡዕ ብሂል ፡፡”

==========================================
አማርኛ ትርጉም
“በኋላ ዘመን በሥጋ የተወለደ ፤ ከእግዚአብሔር አብ በሚገኝ ክብር በዚህ ዓለም የከበረው ፤ ክርስቶስ የተባለው እርሱ ነው ፡፡ በሌላም አይደለም ስለተቀባ ነው እንጅ ፤ ክርስቶስ ማለት የተቀባ ማለት ነውና”
================================
የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ትርጉም
“ዘተወልደ በደኃሪ መዋዕል በሥጋ ፤ ወከብረ በዝንቱ ዓለም በዘይትፌኔ እምኀበ እግዚአብሔር አብ፤ ወተሰምየ ክርስቶስ ፤ አኮ በእን ካልዕ ፤ አላ በእንተ በዘተሰብአ ፤ እስመ ክርስቶስ ብሂል አሐዱ እምክልኤቱ ብሂል፤
የአማርኛ ትርጉማቸው፡
“በኋላ ዘመን በሥጋ የተወለደ ፤ ከአብ በሚገኝ ክብር በዚህ ዓለም የከበረው እሱ ነው ፡፡ ከአብ የተገኘም ክብር አካለ ቃል ነው ፡፡ ክርስቶስ ተባለ ፤ በኅድረት አይደለም ፤ ቢዋሐድ ነው እንጅ ፤ ክርስቶስ ማለት በተዋሕዶ ከበረ ማለት ነውና” ብለውታል ፡፡
==============================

የተቀብዐ ጾመኞችና ሩጫቸው (ክፍል አንድ)

ቄርሎስ ስለ ክርስቶስ ተቀባዒነት ከተናገረው

=====+====+===
“እመ ይሬስዮሙ ለመላእክቲሁ መንፈሰ (መላእክትን በዓይን የማይታዩ በእጅ የማይዳሰሱ ረቂቃን አድርጎ የፈጠራቸው ከሆነ ፤ አንድም የፈጠራቸው ሲሆን) ፤ ወመንበር ቦቱ ዘመለኮት (የአምላክነት ሥልጣን ገንዘቡ ከሆነ ፤ አንድም ገንዘቡ ሲሆን) ፤ በእንተ ምንት ተቀብዐ ቅብዓ ትፍሥሕት (እንደምን የደሥታ ዘይትን ተቀባ/ከበረ ብትል) ፤ ወይፈጥር መላእክተ ከመ አምላክ ውእቱ (የባሕርይ አምላክ ነውና መላእክትን ፈጠረ) ፤ ወተቀብዓ ከመ ሰብእ (ሰው በመሆኑ ተቀባ ከበረ) ፤ አኮ በህላዌ መለኮት (በባሕርየ መለኮቱ አይደለም) ፤ አላ ተሰጊዎ ነሥአ ቅብዓተ በሥምረቱ አምላክ ወሰብእ ክርስቶስ (በፈቃዱ ሰው በሆነ ጊዜ ተቀባ ከበረ ተባለ እንጅ ፤ ክርስቶስ አምላክ ነው ሰውም ነው እልሃለው)”
ብራና ምቅዋም 20 ላይ ይገኛል ፡፡ ምቅዋም ማለት ምዕራፍ እንደማለት ነው ፡፡