በስመ
አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!
ክፍል ሦስት
======+====
ይድረስ ለ “frehiwot aregie”
ክፍል ሦስት
======+====
ይድረስ ለ “frehiwot aregie”
========+==========
1ኛ‹‹‹‹‹‹‹
“3ኛ ንባብ ቅብዓ መንፈስ ቅዱስ ነው ያለው ሲተረጉም የመንፈስ ቅዱስ ቅብአት ተብሎ እንጅ ቅብአት ያለው መንፈስ ቅዱስ አይደለም” ›››››››››››››ብለሃል ፤
ወዳጃችን አክሲማሮስ እየነገረን ያለው “ወአንትሙሰ ቅብዓት ብክሙ እምነ መንፈስ ቅዱስ” እንዳለ ፤ ሕዝቡ አሕዛቡ የጸጋ ልጅነት
የተወለድንበት እርሱ መድኅን ክርስቶስ በማኅፀነ እሙ ሰው ስለመሆኑ በሰውነቱ ልደት ባሕርያዊትን ከአብ የተወለደበት ቅብዓቱ
መንፈስ ቅዱስ እደሆነ ነው ፡፡ “ይህ ቅብዓት ምንድን ነው ቢሉ መንፈስ ቅዱስ ነው” ብሎ እየነገረን ሳለ ልቡናን እንደፈርዖን
ማደንደን አይጠቅምህም ፡፡
2ኛ‹‹‹‹‹‹‹ “4ኛ ለቅዱሳት መጻሕፍት ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ መስጠት ልማድ ነው ።ወልህቀ በመንፈስ ቅዱስ በመንፈስ ቅዱስ አደገ መንመንፈስ ቅዱስ አደረባት እያለ ረቂቁን የመይመረመር ነገር ሁሉ ለመንፈስ ቅዱስ ይሰጣልና ። ስለዚህ ቅብአት ነን ባዮች አስተውሉ”›››››››››››››ብለሃል ወዳጃችን እኛ አንተ ሳትነግረን ቅዱስ መጽሐፍ ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ እየሰጠ እንዲናገር በደንብ እናውቀዋለን ፡፡ አስተውል ! መጻሕፍት ረቂቁን ነገር ለመንፈስ ቅዱስ መስጠታቸው እኛ ሰዎች ሥራችንን የምንሰራው በነፍሳችን ሕያዋን ሁነን እንደሆነ ሁሉ ሥላሴም ማንኛውንም ሥራቸውን ሲያከናውኑ በመንፈስ ቅዱስ ሕያው ሁነው ነውና ስለዚህ ነው ፡፡