ከክፍል አንድ በቀጥታ የቀጠለ
ዜና ትንሣኤሁ ለኢየሱስ ክርስቶስ (ክፍል አንድ )
እነሆ የክርስቶስን ትንሣኤ የሚያወሱ ዐበይት ቃላትን ከዕለቱ ሥርዓተ ቅዳሴና የዋዜማ ሥርዓት ለአዘክሮት እንመልከት ፡፡
“የመጀመሪያው (ከቅዳሴ በፊት የሚሰበከው ምስባክ)
==============================
“ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም
ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን
ወቀተለ ጸሮ በድኅሬሁ”
መዝሙር 77 ፡65
አንድምታ ትርጉም
“ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃህ እምንዋም ፤ ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን ፤ ወቀተለ ጸሮ በድኅሬሁ” ”
የተኛ ሰው ፈጥኖ እንደሚነሳ እግዚአብሔርም ከሰባ ዘመን በኋላ ፈጥኖ በረድኤት ተነሣ
ከመ ዘኃደጎ ሥካረ ወይን ይላል አብነት የወይን ሥካር እንዳለፈለት ሰው አንድም ከመ ኅዱግ ወይን ይላል አበርትቶ እንደተጣላ ወይን ፡፡ በሀገራቸው ፅኑ መጠጥ አለ ሰው የጠጣው እንደሆነ ሦስት ቀን ወድቆ ይሰነብታል ፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)