ጾመ ነቢያት መቼና ለምን?

 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

=====+=====+====
ጾመ ነቢያት መቼ ፤ ለምን ( ክፍል አንድ)
====+===+====
ኦርቶዶክሳዊው ጾመ ነቢያት በዐራቱም ዘመናት (በማቴዎስ ፣ በማርቆስ ፣ በሉቃስ ፣ በዮሐንስ) ኅዳር 19 ቀን ይገባል ታኅሣሥ 29 ይፈታል።
------------------------------------------------------------
ልዑለ ባሕርይ ቅዱስ እግዚአብሔር አዳምን በአርያውና በአምሳሉ ፈጥሮ በፈጠረው በ40 ቀኑ በመንፈስ ቅዱስ አክብሮ ገነት አስገባው ፡፡ አዳም ግን በደለ ፤ ከገነትም ተባረረ ፤ በምድረ በዳዋ በደብረ ቅዱስም ተቀመጠ ፤ በጥንተ ጠላቱ ሠይጣንም ሥቃይና መከራን ተቀበለ ፡፡
በዚህም አንጻር በ40 ቀኑ ያጣትን ገነትን ያወርሰው ዘንድ ፤ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ይወርዳል ይወለዳል ፤ አዳምንም ከግዞት ከባርነት ነጻ ያወጣዋል ብለው ነቢያት የጾሙት ጾም ነው ፡፡ ጾሙ 40 መዓልት 40 ሌሊት ነው ፡፡ “ጾመ ሙሴ ዐርብዓ መዓልተ ወዐርብዓ ሌሊተ” እንዳለች ኦሪት ፡፡ ከ40 ቀን በላይ ጾመ ተብሎ የተጻፈለት አንድም ነቢይ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አይገኝም ፡፡ 40 ቀን የሚሆነው ጾሙን ኅዳር 19 ስንጀምር ነው ፡፡

ነገር ግን “62ኛው የግብጽ ጳጳስ አብርሃም ሶርያዊ ሦስት ቀን በመጾም ተራራ አንቀሳቅሶ ከመናፍቃን ሕዝቡን ያዳነባት ጾም ናትና ከ40ው ጾም ጋር መጨመር አለባት” እያሉ የሚከራከሩ ሰዎች አሉ ፡፡

መዝሙረ ዳዊት የብራና ትርጓሜ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
-----------ትዝብት------------
መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ፡
መተርጉማኑ መዝሙር ሁለትን በተረጎሙበት አምድ ላይ
“ላዕለ እግዚአብሔር ወላዕለ መሢሁ” የሚለውን ገጸ ንባብ
አንድ ጊዜ “በእግዚአብሔርና በመሢሁ ላይ” ብለው ሲያልፉት ሌላ ጊዜ ደግሞ “በእግዚአብሔር አብና በእግዚአብሔር ወልድ ላይ” እያሉ ዋናዋን ቃል ላለመንካት ዳር ዳር በማለት ሲተረጉሙት በብራ የተጻፈው ትርጓሜ ላይ ግን “በእግዚአብሔር አብም መንፈስ ቅዱስን በቀባው ልጁም” በማለት ተተርጉሞ ይገኛል። ይህ ትርጓሜም የእነ ቅዱስ ቄርሎስን፣ የእነ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን ትርጓሜ የተከተለ ሆኖ እናገኘዋለን። ይህም ማለት እንግዲህ ከስሙ ትርጓሜ ስንነሳ
ክርስቶስ - በጽርዕ፤
መሲሕ - በአረብ፤
ቅቡዕ - በግእዝ፤
የተቀባ - በአማረኛ ተብሎ ተተርጉሞ በመጽሐፍት እናገኘዋለንና። ዮሐ ፩፥፵፩ ትርጓሜ፤ መጽ ምስጢር 20፥40።
ሌላው ደግሞ መዝሙር 44 ላይ ነቢዩ ቅዱስ ዳዊት ስለ ክርስቶስ የተናገረበት ትንቢት ነው።
“መዝሙረ ዳዊት ንባቡና ትርጓሜው” በማለት በ1950 ዓ/ም የታተመውና ከዚያ ጀምሮ ወልድ ቅብዕ ባዮች(ካሮች) “ከጥንት ከኢትዮጵያ ሊቃውንት ሲወርድ ሲዋረድ እንደመጣ” በማለት በማር የተለወሠ መርዛቸውን ለትውልድ ሲግቱ እንደሚከተለው እናየዋለን።
"ተከዕወ ሞገስ እምከናፍሪከ ፤ በእንተዝ ባረከከ እግዚአብሔር ለዓለም -- ካንደበትህ ባለሟልነት ሞልቶ ፈሰሰ፤ ስለዚህ ነገር እግዚአብሔርነትህ ለዘላለሙ በተዋሕዶ አከበረህ” ብለው የሌለ ትርጉም፤ እንግዳ ትምህርት በማስገባት ተርጉመውታል።
ከብራናው ላይ ግን ““ተከዕወ ሞገስ እምከናፍሪከ --
ስርየተ ኃጢያት፤ ትምህርት ከአፍህ እንደ ውኃ ፈሰሰ።
በእንተዝ ባረከከ እግዚአብሔር ለዓለም --- ኃጢያት ታስተሰርይ፣ ታምራትም ታደርግ ዘንድ፤ ትምህርትም እንድታስተምር በቅብዓተ መንፈስ ቅዱስ አከበረህ” ይላል።

የግንደ ወይን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ታሪክ

 


የግንደ ወይን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ታሪክ

የደብረፅዮን ቅድስት ማርያም ገዳም የምትገኘው በግንደወይን ከተማ ሲሆን፤ ጊዜው 1500 ዓ.ም ነው በዚህን ወቅት በዚች ላይ የአባ እንጦንዮስ እና የአባ መቃርዮስን ስርዓተ ምንኩስናና ብህቱና ተቀብለው አለምን ንቀው በህብረት የሚያገለግሉ መናኒያን ድምፀአራዊቱን ግርማ ሞገሱን ታግሰው ታቦተ ኪዳንምህረትን ይዘው ይኖሩ ነበር ፡፡

ዋቢ መጽሐፍት

 1. መጽሐፈ ዲድስቅልያ        view

2. ፍትሐ ነገስት          view

3. ድርሳነ ዮሐንስ አፈ ወርቅ        view

4. መጽሐፈ ምስጢር         view

5. መጽሐፈ አክሲማሮስ     view 

6. ሃይማኖተ አበው      መግቢያ    ክፍል 1     ክፍል 2    

                              ክፍል 3   ክፍል 4    ክፍል 5   ክፍል 7

7. የቅዱስ ወንጌል አንድምታ    View

8.  ወልደ አብ      view

9.  ክርስቶስ    view

10. መድሎተ አሚን    view

11. ሃይማኖተ አበው ቀደምት (ኪ/ወ ክፍሌ)     ክፍል 1     ክፍል 2   

12. ፈለገ ጥበብ መጽሔት    view

13. ዜና ቤተ ክርስቲያን ጋዜጣ   view

    ይህ ጋዜጣ በ 2008 ዓ/ም የታተመ ሲሆን  ልደተ ክርስቶስ በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 መከበር እንዳለበት መወሰኑን የሚናገር  ነው።